የልጄን ፓስፖርት መፈረም ያለበት ማነው?

ዕድሜያቸው 14 እና ከዚያ በላይ የሆኑ ልጆች የራሳቸውን ፓስፖርት መፈረም ይችላሉ። ከ14 ዓመት በታች ለሆኑ ህጻናት ወላጅ መፈረም አለበት። ለፊርማው በተዘጋጀው ቦታ ላይ ወላጅ ወይም ህጋዊ አሳዳጊ የልጁን ስም በማተም የራሱን/የራሷን ስም መፈረም አለባቸው። ከዚያም፣ በቅንፍ ውስጥ ፓስፖርቱን የፈረመው ማን እንደሆነ እንዲታወቅ ከህጻኑ ጋር ያላቸውግንኙነት፣ ማለትም (እናት) ወይም (አባት) መፃፍ አለባቸው።